No survivors in Lebanon crash: Officials
BEIRUT – An Ethiopian Airlines plane carrying 90 people caught fire and crashed into the sea minutes after taking off from Beirut early Monday, setting off a frantic search as passenger seats, baby sandals and other debris washed ashore. At least 34 bodies were recovered.
http://www.ethiomedia.com/course/5125.html
Monday, January 25, 2010
እያንጓለለ! (የምርጫ ጭውውት)
እያንጓለለ!
ያ ገብስማ ዶሮ- ዘንድሮስ ምን አለ?
ሊቀ መኳስ ቆመ- አራት ኪሎ ላይ
ትናንት መለስ መለስ…
ዛሬም መለስ መለስ…
ነገም መለስ መለስ- መለስ መለስ ባይ።
አገር አሳደጉ
ሰላም አወረዱ
ይህን አድርገዋል -ስሙ ያልሰማችሁ
ተገቢ ነውና-በሙሉ ድምጻችሁ
ለዘንድሮው ምርጫ-እነርሱን ባትመርጡ
ትዝብት ነው እንጅ-ምንም አታመጡ።
ኩኩሉ አለ ዶሮ
የምን ምርጫ ነው ዘንድሮ
ውጤቱን ያወቅነው ገና ዱሮ
መለስ ሊመረጥ ዞሮ ዞሮ!
እያንጓለለ!
ያ ገብስማ ዶሮ- ዘንድሮስ ምን አለ?
መሪው ሊቀ መኳስ-አጭር ሰው መላጣ
“ላሌ ላሌ” እያለ- ይኸውና መጣ።
“ቂ! ቂ!....
ልደቱ ልደቱ- እያሉ ሲያለቅሱ
እነኃይሉም መጡ- ከእኔ ሊቋደሱ”
ኩኩሉ አለ ዶሮ
ማን ነው የሚገደል ዘንድሮ
ማን ነው አስገዳይ ዘንድሮ
እያንጓለለ!
ያ ገብስማ ዶሮ- ዘንድሮስ ምን አለ?
ያዝ ልደቱ…
አውቄ ነው እንጅ ድሮም ስግደረደር
እኔስ ለአድዋው ሰው-አሽከር ሆኘ ልደር
እንደምን ነው ስሜን-ወገብ ለወገቡ
እንደምን ነው ትግራይ-ወገብ ለወገቡ
የእነአዜብዬ አገር- የእነአይጠገቡ
አላማጣ ውዬ- መልሸ አላማጣ
ሽህ ሰው ይተላለቅ- እናንተን ከማጣ
እኔስ በመለስ ላይ- ክፉም አላመጣ።
ኩኩሉ አለ ዶሮ
ምን ተደግሶልናል ዘንድሮ
እያንጓለለ!
ያ ገብስማ ዶሮ- ዘንድሮስ ምን አለ?
ያዝ መለስ..
ብለነው ብለነው- የተውነውን ነገር
አምና ኃይሉ ስምቶ- ታንቆ ሊሞት ነበር
ዘንድሮ መምጣቱ- መስማማቱ ላይቀር
ልደቱን መውቀሱ- ተገቢም አልነበር።
አገራችን ትግራይ- ወንዛችን ተከዜ
ማነው እምቢ የሚል- ምርጫ ባልን ጊዜ።
እያንጓለለ!
ያ ገብስማ ዶሮ- ዘንድሮስ ምን አለ?
ኩኩሉ አለ ዶሮ
ኃይሉስ ምን አለ ዘንድሮ
በእስር በእንግልቴ- ሁሉ እማስብሽ
እኔም ልመጣ ነው ፓርላማ እንዴት ነሽ?
ኤልያስ የሚሉት-የሻዕቢያ ምላስ
መለስ ጠላት ብሎ-ሕዝብን ሲቀስቅስ
እኔም ወንድነቴ-ነሸጥ አድርጎኝ
ፓርላማ መግባቴ-ውርደት ነው አልኩኝ
ያ ክፉ ባለጌ- አሳሳተኝና
ባለፈው ባልመጣ- ባላይሽ ታችሃምና
ዘንድሮ ቁርጥ ነው-እንገናኛለን
እንዲህ ተለያይተን -መች እንቀራለን
መልክ ሰጠኝ እንጅ- ሲሉ እስማ ነበር
ሙያ ከልደቱ- ይኸው ጀመርኩ መማር።
እኔም ላሞግሰው-ልነሳ አደግድጌ
የአድዋው ሰውዬ- ባይሆን አብሮ አደጌ
አክብሮ ጥሪዬን- እጀን ሲጨብጠኝ
ከእራሴ ጀምሮ-ወገቤን ነዘረኝ::
ደጋፊ አስፈልጎኝ- በጋሪ ስገፋ
መለስን ስጨብጥ- በሽታዬ ጠፋ::
ይኸው መፎከሬ- “መለስ ይውረድ” ቀርቶ
ሰላም ሰላም ሆኗል- የዘንድሮው motto::
እኔ ፍራሽ ሆኘ- ልደቱ ትራስ
እንጠብቃለን- አልጋህ እንዳይፈርስ።
እያንጓለለ!
ያ ገብስማ ዶሮ- ዘንድሮስ ምን አለ?
ኩኩሉ አለ ዶሮ
በየነስ ምን አለ ዘንድሮ
ዓመት አስር ዓመት- የደነስኩብሽ
አንች ዉቧ ቆንጆ- ፓርላማ እንዴት ነሽ
ህዝቡ ቢቃወመኝ- አትግባ ቢለኝም
እመኝኝ ፓርላማ- ከአንች አልለያይም::
ዘጠና ሰባትን- ጠፍቶ እሚገድብ
ቅንጅት ተፈጥሮ -ወጣና ከህዝብ
ለጥቂት ተረፍኩኝ- ዱላ ከሚመዝ
ዳግመኛ እንዳይመጣ- ያን መሳይ መዘዝ።
ወያኔ ስትዳር- ጎጆ ስትቀልስ
ያን ጊዜ ጀምሮ-እስካሁን ድረስ
ታማኝ ተቃዋሚ-ሆኘ ለመለስ
መልካም ተብሎ ለእኔ- ህዝብም ተዘናግቶ
ያልፈኛል ሁልጊዜ- እንዳላዬኝ አይቶ።
ኩኩሉ አለ ዶሮ
ምን መዓት ይመጣል ዘንድሮ
እያንጓለለ!
ያ ገብስማ ዶሮ- ዘንድሮስ ምን አለ?
ያዝ ኃይሉ…
አድዋ ላይ ሆኖ- መለስ ቢደነፋ
ብርሃኑ ነጋ- አገር ጥሎ ጠፋ
ድሮም በእጀ- ያልኩት መስፍንን አምኘ
ያኔ እርሱን ማመኔም- ፍፁም የዋህ ሆኘ
“በብልቃጥ ተረግዞ- መስታወት ተወልዶ”
ድርጀት መባሉም- ወይ ነዶ ወይ ነዶ
እንግዲህስ በቃኝ- መስፍን የለ ሌላ
ጠቃሚ ላይሆኑ- የኋላ የኋላ
ፓርላማው ሰፊ ነው- ቧ ያለው መንገዱ
ስነ ምግባር ብቻ መፈረም ነው ኮዱ።
ቀብቸ አሽሞንሙኘ- ከላይ ባረግሽ
አምባ ገነን ብለሽ- ስሜን አጠፋሽ
በገዛ ምላሷ- በገዛ አንደበቷ
ቃሊቲ ገብታለች- ከዘላለም ቤቷ
አትሳቂ እያልኳት- ባህር ማዶ ስቃ
አመጣችው እስሩን- ነቅንቃ ነቅንቃ።
ኩኩሉ አለ ዶሮ
በችግር ላይ ችግር ሆኖ የእኛ ኑሮ
እያንጓለለ!
ያ ገብስማ ዶሮ- ዘንድሮስ ምን አለ?
ያዝ ብርሃኑ…
ስሙልኝ ይኸን ሰው- እዩት ስም ሲያጠፋ
ምርጫ ውሸት ነው ብል-አለኝ ጥሎ ጠፋ
እኔስ ያከበርኩህ- በሽምግልናህ ነው
አመራር ሲመጣ- ጉድክን ሳስተውለው
አምባገነንነት- ፍጹም መለያህ ነው
እነ መለስ ዜና -ሰይጣን መርቋቸው
ተቃዋሚ ጀባ- ብለው በጫታቸው
አንገዋለለና-ልደቱን ሰጣቸው
አንገዋለለና- በየነን ሰጣቸው
አንተን በምራቂ- ይኸው ጨመራችው
እያንጓለለ!
ያ ገብስማ ዶሮ- ዘንድሮስ ምን አለ?
ያዥ ብርቱካን…
ዓለም ዓለም…ዓለም ዓለምዬ
እሽሩሩ ስቃይ- ውረድ ከጀርባዬ
ደብተራው የማነ-- አረጋሽ እህቴ
አብረው የሚኖሩ- ቤታቸው ከቤቴ
የእግዜር ፈቃድ ሆኖ- ቢሰማ ጸሎቴ
ለፍች ያብቃችሁ- ከአላማችሁ ግብ
አምላክ ያውርድና- የሰላም ድባብ።
ዛሬ በመልዓኩ- በገብርኤል በበዓሉ
ወዲ መለስ ዜና- መሽረብ ጀመረ አሉ
ኃይሉ መላጣ ላይ- ሽሩባ ጎንጉኖ
“እኔን እኔን ስራኝ” ይላል ልደት አብሮ
ጸጉር እንዲህ ይሰራል- ከክዳን ጀምሮ።
ተወኝ አላልኩም ወይ- ይህን ዓመልህን
ልክ እንደልደቱ- አንተም መክዳትህን
ልደቱስ ቢያንስ እንኳን- ይሄድ ይመለሳል
ምርጫ መጣ ሲሉት- መለስን ይወቅሳል።
እያንጓለለ!
ያ ገብስማ ዶሮ- ዘንድሮስ ምን አለ?
*********
ኩኩሉ አለ ዶሮ
አራት ኪሎ አስመራን ምን ይላል ዘንድሮ
ያዝ መለስ…
ከሰማዩ በላይ- ያለኸው ሰማይ
ወዲ አፎም በጤናው- ዘግቶኝ ቀረ ወይ
ደግሞ በዚህ ምርጫ ያደናቅፍ ወይ?
የቀይ ዳማ ረጅም- ጎራዴ ታጣቂ
ልግደልህ እያለኝ- እኔ እርሱን ናፋቂ
እያንጓለለ!
ያ ገብስማ ዶሮ- ዘንድሮስ ምን አለ?
ኩኩሉ አለ ዶሮ
ኢሳያስ ምን ይላል ዘንድሮ
ልቤ አብጦ ጀግኘ- አንበሳ ነኝ ስል
ጦር አዘመትክና- አደረከኝ ድል
አስራ ሁለት ሌሊት- አስራ ሁለት ቀን
ከትግራይ ተነስትህ- ልትይዝ አስመራን
ጉዴ ፈልቶ ነበር- ክሊንተን ባይኖር
ያስጎራሃል አሉ- በየአምስት ዓመት
ደም የለመደ እጅህ- ሲሻ መስዋዕት
ሲሉ ሰምታ ሆኖ- ሆነና ነገሩ
ምዕራብ ያለው ሁሉ- ይመስልሃል ጥሩ።
ምርጫ ምርጫ-ብለህ ብትፈጥር ግርግር
እኔ ጌታህ ሆኘ- ካልሆንከኝ አሽከር
ውጊያ መቀስቀሱ- ምንጊዜም አይቀር።
እያንጓለለ!
ያ ገብስማ ዶሮ- ዘንድሮስ ምን አለ?
ያዝ መለስ
ጠያቂው ቢያስጨንቀኝ- ስለኤርትራ ሁኔታ
አልወዳትም አልኳቸው- እንዲያገኙ ፋታ።
ቁርጡማ ሲመጣ- አስመራ ልትያዝ
የኔ ተግባር ነበር- እነስየን ማዘዝ
አልጀርስ ሳገኝህ- ውል ልትፈራርም
አልንበረምና- እኔ ያልኩኝ ጥምጥም
ይናፍቃል ላካስ- እንደዚያ ዎንድም።
እያንጓለለ!
ያ ገብስማ ዶሮ- ዘንድሮስ ምን አለ?
ያዝ ስዬ…
ተወኝ አላልኩም ወይ- ይህን አመልህን
ጫት እንዳዬ ጀዝባ- አስመራን መዞርክን
ጫትን ያዬ ቃሚስ- ቅሞ ይመለሳል
የአንተ ሁኔታ ግን- ግራ ነው እሚያጋባን።
እያንጓለለ!
ያ ገብስማ ዶሮ- ዘንድሮስ ምን አለ?
ኩኩሉ አለ ዶሮ
ህዝባችን ምን አለ ዘንድሮ
የሚመጣው ምርጫ- ምኞታችሁ መክኖ
የፍትህ አካላት- ፕሬስ ነጻ ሆኖ
ገለልተኛ ሆኖ- መከላከያችን
ገለልተኛ ሆኖ- የምርጫ ቦርዳችን
በነጻ እንዲስማ- እንደ ህዝብ ድምጻችን
በዘር በሃይማኖት- መጋጨት ትታችሁ
ኤርትራና ትግራይ
አማራ ኦሮሞ ማለቱን ትታችሁ
አብዮት-- አብዮት ማለት አቁማችሁ
ሁላችንን በእኩል- ሕጉ እንዲመዝነን
የስልጣኑ ምንጮች- እኛ ህዝቡ እንሁን።
ዳግማዊ ዳዊት
ጥር 2002
ያ ገብስማ ዶሮ- ዘንድሮስ ምን አለ?
ሊቀ መኳስ ቆመ- አራት ኪሎ ላይ
ትናንት መለስ መለስ…
ዛሬም መለስ መለስ…
ነገም መለስ መለስ- መለስ መለስ ባይ።
አገር አሳደጉ
ሰላም አወረዱ
ይህን አድርገዋል -ስሙ ያልሰማችሁ
ተገቢ ነውና-በሙሉ ድምጻችሁ
ለዘንድሮው ምርጫ-እነርሱን ባትመርጡ
ትዝብት ነው እንጅ-ምንም አታመጡ።
ኩኩሉ አለ ዶሮ
የምን ምርጫ ነው ዘንድሮ
ውጤቱን ያወቅነው ገና ዱሮ
መለስ ሊመረጥ ዞሮ ዞሮ!
እያንጓለለ!
ያ ገብስማ ዶሮ- ዘንድሮስ ምን አለ?
መሪው ሊቀ መኳስ-አጭር ሰው መላጣ
“ላሌ ላሌ” እያለ- ይኸውና መጣ።
“ቂ! ቂ!....
ልደቱ ልደቱ- እያሉ ሲያለቅሱ
እነኃይሉም መጡ- ከእኔ ሊቋደሱ”
ኩኩሉ አለ ዶሮ
ማን ነው የሚገደል ዘንድሮ
ማን ነው አስገዳይ ዘንድሮ
እያንጓለለ!
ያ ገብስማ ዶሮ- ዘንድሮስ ምን አለ?
ያዝ ልደቱ…
አውቄ ነው እንጅ ድሮም ስግደረደር
እኔስ ለአድዋው ሰው-አሽከር ሆኘ ልደር
እንደምን ነው ስሜን-ወገብ ለወገቡ
እንደምን ነው ትግራይ-ወገብ ለወገቡ
የእነአዜብዬ አገር- የእነአይጠገቡ
አላማጣ ውዬ- መልሸ አላማጣ
ሽህ ሰው ይተላለቅ- እናንተን ከማጣ
እኔስ በመለስ ላይ- ክፉም አላመጣ።
ኩኩሉ አለ ዶሮ
ምን ተደግሶልናል ዘንድሮ
እያንጓለለ!
ያ ገብስማ ዶሮ- ዘንድሮስ ምን አለ?
ያዝ መለስ..
ብለነው ብለነው- የተውነውን ነገር
አምና ኃይሉ ስምቶ- ታንቆ ሊሞት ነበር
ዘንድሮ መምጣቱ- መስማማቱ ላይቀር
ልደቱን መውቀሱ- ተገቢም አልነበር።
አገራችን ትግራይ- ወንዛችን ተከዜ
ማነው እምቢ የሚል- ምርጫ ባልን ጊዜ።
እያንጓለለ!
ያ ገብስማ ዶሮ- ዘንድሮስ ምን አለ?
ኩኩሉ አለ ዶሮ
ኃይሉስ ምን አለ ዘንድሮ
በእስር በእንግልቴ- ሁሉ እማስብሽ
እኔም ልመጣ ነው ፓርላማ እንዴት ነሽ?
ኤልያስ የሚሉት-የሻዕቢያ ምላስ
መለስ ጠላት ብሎ-ሕዝብን ሲቀስቅስ
እኔም ወንድነቴ-ነሸጥ አድርጎኝ
ፓርላማ መግባቴ-ውርደት ነው አልኩኝ
ያ ክፉ ባለጌ- አሳሳተኝና
ባለፈው ባልመጣ- ባላይሽ ታችሃምና
ዘንድሮ ቁርጥ ነው-እንገናኛለን
እንዲህ ተለያይተን -መች እንቀራለን
መልክ ሰጠኝ እንጅ- ሲሉ እስማ ነበር
ሙያ ከልደቱ- ይኸው ጀመርኩ መማር።
እኔም ላሞግሰው-ልነሳ አደግድጌ
የአድዋው ሰውዬ- ባይሆን አብሮ አደጌ
አክብሮ ጥሪዬን- እጀን ሲጨብጠኝ
ከእራሴ ጀምሮ-ወገቤን ነዘረኝ::
ደጋፊ አስፈልጎኝ- በጋሪ ስገፋ
መለስን ስጨብጥ- በሽታዬ ጠፋ::
ይኸው መፎከሬ- “መለስ ይውረድ” ቀርቶ
ሰላም ሰላም ሆኗል- የዘንድሮው motto::
እኔ ፍራሽ ሆኘ- ልደቱ ትራስ
እንጠብቃለን- አልጋህ እንዳይፈርስ።
እያንጓለለ!
ያ ገብስማ ዶሮ- ዘንድሮስ ምን አለ?
ኩኩሉ አለ ዶሮ
በየነስ ምን አለ ዘንድሮ
ዓመት አስር ዓመት- የደነስኩብሽ
አንች ዉቧ ቆንጆ- ፓርላማ እንዴት ነሽ
ህዝቡ ቢቃወመኝ- አትግባ ቢለኝም
እመኝኝ ፓርላማ- ከአንች አልለያይም::
ዘጠና ሰባትን- ጠፍቶ እሚገድብ
ቅንጅት ተፈጥሮ -ወጣና ከህዝብ
ለጥቂት ተረፍኩኝ- ዱላ ከሚመዝ
ዳግመኛ እንዳይመጣ- ያን መሳይ መዘዝ።
ወያኔ ስትዳር- ጎጆ ስትቀልስ
ያን ጊዜ ጀምሮ-እስካሁን ድረስ
ታማኝ ተቃዋሚ-ሆኘ ለመለስ
መልካም ተብሎ ለእኔ- ህዝብም ተዘናግቶ
ያልፈኛል ሁልጊዜ- እንዳላዬኝ አይቶ።
ኩኩሉ አለ ዶሮ
ምን መዓት ይመጣል ዘንድሮ
እያንጓለለ!
ያ ገብስማ ዶሮ- ዘንድሮስ ምን አለ?
ያዝ ኃይሉ…
አድዋ ላይ ሆኖ- መለስ ቢደነፋ
ብርሃኑ ነጋ- አገር ጥሎ ጠፋ
ድሮም በእጀ- ያልኩት መስፍንን አምኘ
ያኔ እርሱን ማመኔም- ፍፁም የዋህ ሆኘ
“በብልቃጥ ተረግዞ- መስታወት ተወልዶ”
ድርጀት መባሉም- ወይ ነዶ ወይ ነዶ
እንግዲህስ በቃኝ- መስፍን የለ ሌላ
ጠቃሚ ላይሆኑ- የኋላ የኋላ
ፓርላማው ሰፊ ነው- ቧ ያለው መንገዱ
ስነ ምግባር ብቻ መፈረም ነው ኮዱ።
ቀብቸ አሽሞንሙኘ- ከላይ ባረግሽ
አምባ ገነን ብለሽ- ስሜን አጠፋሽ
በገዛ ምላሷ- በገዛ አንደበቷ
ቃሊቲ ገብታለች- ከዘላለም ቤቷ
አትሳቂ እያልኳት- ባህር ማዶ ስቃ
አመጣችው እስሩን- ነቅንቃ ነቅንቃ።
ኩኩሉ አለ ዶሮ
በችግር ላይ ችግር ሆኖ የእኛ ኑሮ
እያንጓለለ!
ያ ገብስማ ዶሮ- ዘንድሮስ ምን አለ?
ያዝ ብርሃኑ…
ስሙልኝ ይኸን ሰው- እዩት ስም ሲያጠፋ
ምርጫ ውሸት ነው ብል-አለኝ ጥሎ ጠፋ
እኔስ ያከበርኩህ- በሽምግልናህ ነው
አመራር ሲመጣ- ጉድክን ሳስተውለው
አምባገነንነት- ፍጹም መለያህ ነው
እነ መለስ ዜና -ሰይጣን መርቋቸው
ተቃዋሚ ጀባ- ብለው በጫታቸው
አንገዋለለና-ልደቱን ሰጣቸው
አንገዋለለና- በየነን ሰጣቸው
አንተን በምራቂ- ይኸው ጨመራችው
እያንጓለለ!
ያ ገብስማ ዶሮ- ዘንድሮስ ምን አለ?
ያዥ ብርቱካን…
ዓለም ዓለም…ዓለም ዓለምዬ
እሽሩሩ ስቃይ- ውረድ ከጀርባዬ
ደብተራው የማነ-- አረጋሽ እህቴ
አብረው የሚኖሩ- ቤታቸው ከቤቴ
የእግዜር ፈቃድ ሆኖ- ቢሰማ ጸሎቴ
ለፍች ያብቃችሁ- ከአላማችሁ ግብ
አምላክ ያውርድና- የሰላም ድባብ።
ዛሬ በመልዓኩ- በገብርኤል በበዓሉ
ወዲ መለስ ዜና- መሽረብ ጀመረ አሉ
ኃይሉ መላጣ ላይ- ሽሩባ ጎንጉኖ
“እኔን እኔን ስራኝ” ይላል ልደት አብሮ
ጸጉር እንዲህ ይሰራል- ከክዳን ጀምሮ።
ተወኝ አላልኩም ወይ- ይህን ዓመልህን
ልክ እንደልደቱ- አንተም መክዳትህን
ልደቱስ ቢያንስ እንኳን- ይሄድ ይመለሳል
ምርጫ መጣ ሲሉት- መለስን ይወቅሳል።
እያንጓለለ!
ያ ገብስማ ዶሮ- ዘንድሮስ ምን አለ?
*********
ኩኩሉ አለ ዶሮ
አራት ኪሎ አስመራን ምን ይላል ዘንድሮ
ያዝ መለስ…
ከሰማዩ በላይ- ያለኸው ሰማይ
ወዲ አፎም በጤናው- ዘግቶኝ ቀረ ወይ
ደግሞ በዚህ ምርጫ ያደናቅፍ ወይ?
የቀይ ዳማ ረጅም- ጎራዴ ታጣቂ
ልግደልህ እያለኝ- እኔ እርሱን ናፋቂ
እያንጓለለ!
ያ ገብስማ ዶሮ- ዘንድሮስ ምን አለ?
ኩኩሉ አለ ዶሮ
ኢሳያስ ምን ይላል ዘንድሮ
ልቤ አብጦ ጀግኘ- አንበሳ ነኝ ስል
ጦር አዘመትክና- አደረከኝ ድል
አስራ ሁለት ሌሊት- አስራ ሁለት ቀን
ከትግራይ ተነስትህ- ልትይዝ አስመራን
ጉዴ ፈልቶ ነበር- ክሊንተን ባይኖር
ያስጎራሃል አሉ- በየአምስት ዓመት
ደም የለመደ እጅህ- ሲሻ መስዋዕት
ሲሉ ሰምታ ሆኖ- ሆነና ነገሩ
ምዕራብ ያለው ሁሉ- ይመስልሃል ጥሩ።
ምርጫ ምርጫ-ብለህ ብትፈጥር ግርግር
እኔ ጌታህ ሆኘ- ካልሆንከኝ አሽከር
ውጊያ መቀስቀሱ- ምንጊዜም አይቀር።
እያንጓለለ!
ያ ገብስማ ዶሮ- ዘንድሮስ ምን አለ?
ያዝ መለስ
ጠያቂው ቢያስጨንቀኝ- ስለኤርትራ ሁኔታ
አልወዳትም አልኳቸው- እንዲያገኙ ፋታ።
ቁርጡማ ሲመጣ- አስመራ ልትያዝ
የኔ ተግባር ነበር- እነስየን ማዘዝ
አልጀርስ ሳገኝህ- ውል ልትፈራርም
አልንበረምና- እኔ ያልኩኝ ጥምጥም
ይናፍቃል ላካስ- እንደዚያ ዎንድም።
እያንጓለለ!
ያ ገብስማ ዶሮ- ዘንድሮስ ምን አለ?
ያዝ ስዬ…
ተወኝ አላልኩም ወይ- ይህን አመልህን
ጫት እንዳዬ ጀዝባ- አስመራን መዞርክን
ጫትን ያዬ ቃሚስ- ቅሞ ይመለሳል
የአንተ ሁኔታ ግን- ግራ ነው እሚያጋባን።
እያንጓለለ!
ያ ገብስማ ዶሮ- ዘንድሮስ ምን አለ?
ኩኩሉ አለ ዶሮ
ህዝባችን ምን አለ ዘንድሮ
የሚመጣው ምርጫ- ምኞታችሁ መክኖ
የፍትህ አካላት- ፕሬስ ነጻ ሆኖ
ገለልተኛ ሆኖ- መከላከያችን
ገለልተኛ ሆኖ- የምርጫ ቦርዳችን
በነጻ እንዲስማ- እንደ ህዝብ ድምጻችን
በዘር በሃይማኖት- መጋጨት ትታችሁ
ኤርትራና ትግራይ
አማራ ኦሮሞ ማለቱን ትታችሁ
አብዮት-- አብዮት ማለት አቁማችሁ
ሁላችንን በእኩል- ሕጉ እንዲመዝነን
የስልጣኑ ምንጮች- እኛ ህዝቡ እንሁን።
ዳግማዊ ዳዊት
ጥር 2002
Monday, January 18, 2010
አልነጋም- ገና ነው!
የሰማይ ኮርኔሥ ሆኖ- ማቅ የመሰለ ደመና
ከታችም አውሎ ነፋስ- ፉጨቱን እያሰማ
አቧራውን አሥነስቶ- ዛፍ ቅርንጫፉን እያሾረ
ዛሩ እንደወረደ ባለአውሌ- አለመጠን እያስጨፈረ
አይን ቢወጉ በማያሳይ- ጥቅጥቅ ባለ ጨላማ
ወዴት ነው መድረሻችን- ጉዟችን የሚያቀና?
ትናንት እንዳስቆመን ዝናብ- ሊዘንብ ሰማዩ አግቶ
ወዴት ነው የምንሄደው- በትናንቱ ምን ታይቶ?
ትርምስምሳችን ወጥቶ- ጨቅይቶ ሳለ መንገዱ
ለይምሰል አይሆንምወይ -ደግመን ዛሬ መሄዱ?
ትናንት መካሪ ጠፍቶ- ሌሊቱ ገና እናዳልነጋ
ጉዞው መርዛም-እሾክ በዝቶበት- ስንቱ ነው የተወጋ?
እኔስ አልምክርውም- የዛሬውን መንገድ
እስኪነጋ እቆያለሁ- ካልሆነብኝ የግድ
አልነጋም ገና- ጨለማ ነው ሌሊት
እነሱንም ንገሩዋቸው- መጓዙን ይተውት
ተከታያቸውን በመሉ- የአውሬ ቀለብ አያርጉት።
ዳግማዊ ዳዊት
Ethio_dagmawi@yahoo.com
ጥር 2002 ዓ.ም.
ከታችም አውሎ ነፋስ- ፉጨቱን እያሰማ
አቧራውን አሥነስቶ- ዛፍ ቅርንጫፉን እያሾረ
ዛሩ እንደወረደ ባለአውሌ- አለመጠን እያስጨፈረ
አይን ቢወጉ በማያሳይ- ጥቅጥቅ ባለ ጨላማ
ወዴት ነው መድረሻችን- ጉዟችን የሚያቀና?
ትናንት እንዳስቆመን ዝናብ- ሊዘንብ ሰማዩ አግቶ
ወዴት ነው የምንሄደው- በትናንቱ ምን ታይቶ?
ትርምስምሳችን ወጥቶ- ጨቅይቶ ሳለ መንገዱ
ለይምሰል አይሆንምወይ -ደግመን ዛሬ መሄዱ?
ትናንት መካሪ ጠፍቶ- ሌሊቱ ገና እናዳልነጋ
ጉዞው መርዛም-እሾክ በዝቶበት- ስንቱ ነው የተወጋ?
እኔስ አልምክርውም- የዛሬውን መንገድ
እስኪነጋ እቆያለሁ- ካልሆነብኝ የግድ
አልነጋም ገና- ጨለማ ነው ሌሊት
እነሱንም ንገሩዋቸው- መጓዙን ይተውት
ተከታያቸውን በመሉ- የአውሬ ቀለብ አያርጉት።
ዳግማዊ ዳዊት
Ethio_dagmawi@yahoo.com
ጥር 2002 ዓ.ም.
Wednesday, December 23, 2009
Bucknell professor gets death sentence from Ethiopia
By Kristen Holmes December 23, 2009
A Bucknell University professor was sentenced yesterday to death in absentia by an Ethiopian court that convicted him of plotting to assassinate government officials.
Berhanu Nega, of Lewisburg, an associate professor of economics at the Union County school, was one of five people to receive death sentences for planning the attack in 2005 when nearly 200 people were killed in postelection violence.
Nega, 51, denied the charges and called the sentence an expected move of a terrorist government.
"By delivering this sentence they are trying to terrorize the population more than anything else," Nega said in a phone interview. "It is their way of telling everybody if you fight for democracy we will kill you, that is the message they are sending."
Nega said he was at home preparing to take his teenage son to a driving test when he received a phone call with the news.
Nega, an exiled opposition leader of the ruling Ethiopian People's Revolutionary Democratic Front, was elected mayor of Addis Ababa in 2005.
He was the first elected mayor in Ethiopia's history, but the ruling party declared victory, and Nega was among 100 opposition leaders arrested and jailed. Nega was held in prison for 21 months.
"At one point I was in one cell with 350 people," Nega said. "There was no air to breathe, and I developed a heart condition because of that."
Since his release, he has urged the United States and other Western countries to back democratic movements in Ethiopia and withdraw support for dictatorships.
Born near Addis Ababa, Nega immigrated to the United States in 1980. He earned his bachelor's degree in economics from the State University of New York at New Paltz and his doctorate in economics at the New School for Social Research in New York.
He joined the faculty at Bucknell in 1990, but commuted to Philadelphia for three years while his wife, Nardos Minasse, studied at the Pennsylvania College of Optometry.
Nega and his family returned to Ethiopia in 1994 because "we thought maybe there would be a chance to serve and help our country," he said. Nega became active in the democratic movement, taught at Addis Ababa University, and was elected mayor in 2005.
During Nega's imprisonment, supporters including Bucknell president Brian C. Mitchell and university faculty members called for his release, said Tom Evelyn, a spokesman for the university.
"He is a professor in good standing at Bucknell and has a long track record of being a distinguished scholar," Evelyn said.
Nega and others eventually were pardoned and freed. Nega and his family returned to Pennsylvania in August 2007, and the professor resumed teaching at Bucknell. Last week, the Ethiopian government revoked Nega's pardon.
Nega is one of four people sentenced to death yesterday who are living in exile, Nega said. The other is jailed in Ethiopia, Nega said. A sentence of life in prison was ordered for 33 others.
Contact staff writer Kristin E. Holmes at 610-313-8211 or kholmes@phillynews.com.
This article contains information from the Associated Press.
---Source: Philadelphia Inquirer
A Bucknell University professor was sentenced yesterday to death in absentia by an Ethiopian court that convicted him of plotting to assassinate government officials.
Berhanu Nega, of Lewisburg, an associate professor of economics at the Union County school, was one of five people to receive death sentences for planning the attack in 2005 when nearly 200 people were killed in postelection violence.
Nega, 51, denied the charges and called the sentence an expected move of a terrorist government.
"By delivering this sentence they are trying to terrorize the population more than anything else," Nega said in a phone interview. "It is their way of telling everybody if you fight for democracy we will kill you, that is the message they are sending."
Nega said he was at home preparing to take his teenage son to a driving test when he received a phone call with the news.
Nega, an exiled opposition leader of the ruling Ethiopian People's Revolutionary Democratic Front, was elected mayor of Addis Ababa in 2005.
He was the first elected mayor in Ethiopia's history, but the ruling party declared victory, and Nega was among 100 opposition leaders arrested and jailed. Nega was held in prison for 21 months.
"At one point I was in one cell with 350 people," Nega said. "There was no air to breathe, and I developed a heart condition because of that."
Since his release, he has urged the United States and other Western countries to back democratic movements in Ethiopia and withdraw support for dictatorships.
Born near Addis Ababa, Nega immigrated to the United States in 1980. He earned his bachelor's degree in economics from the State University of New York at New Paltz and his doctorate in economics at the New School for Social Research in New York.
He joined the faculty at Bucknell in 1990, but commuted to Philadelphia for three years while his wife, Nardos Minasse, studied at the Pennsylvania College of Optometry.
Nega and his family returned to Ethiopia in 1994 because "we thought maybe there would be a chance to serve and help our country," he said. Nega became active in the democratic movement, taught at Addis Ababa University, and was elected mayor in 2005.
During Nega's imprisonment, supporters including Bucknell president Brian C. Mitchell and university faculty members called for his release, said Tom Evelyn, a spokesman for the university.
"He is a professor in good standing at Bucknell and has a long track record of being a distinguished scholar," Evelyn said.
Nega and others eventually were pardoned and freed. Nega and his family returned to Pennsylvania in August 2007, and the professor resumed teaching at Bucknell. Last week, the Ethiopian government revoked Nega's pardon.
Nega is one of four people sentenced to death yesterday who are living in exile, Nega said. The other is jailed in Ethiopia, Nega said. A sentence of life in prison was ordered for 33 others.
Contact staff writer Kristin E. Holmes at 610-313-8211 or kholmes@phillynews.com.
This article contains information from the Associated Press.
---Source: Philadelphia Inquirer
አኬልዳማ
በአገሬ ሕዝብ ላይ- ሰቆቃ
ምነው አልቆም አለ-አላበቃ
ርህራሄ ተነፍጎት-
እየኖረ በዋይታ
ስው ባምሳያው- ሰብዓዊነት
አልሰማው ብሎ-ኃላፊነት
ሰብዓዊ መብቱ- ተረግጦ
ወገን በወገን ላይ-ዶልቶ
ወገን ሞቶ-ወገን ገድሎ
በፉከራ
ፈጣሪም ሳይፈራ
ዘራፍ ብለን ራሳችን- በራሳችን
እኛው በእኛ ላይ- አምፀን
ጳጳስ ገድለን- ጳጳስ ሾመን
አሃዱ ብለን በስልሳ ራስ- አንገት ቀልተን
የኛን ራስ- እኛው ጠልተን
የአስራ ሁለት ዓመት ልጅ -ገና ጨቅላ
የአስር ዓመት ልጃገረድ- እምቦቅላ
ሽኘን በሞት- በሽለላ
ገዳይ ብለን በፉከራ።
ድንበር ሰርተን- ሸሁን ገፍተን- ካህን ጠልተን
በማናውቀው ርዕዮተዓለም- ተጠምቀን
ሽብር ሆኖ ቀይና ነጭ-ወገን ከፍሎ
አንዱ ሌላውን-ሊያጠፋ ተገዝቶ ምሎ
ልንጠፋፋ-ተገዳድረን
በጥፋት ካህን ፊት-ምለን ተገዝተን
ላንተኛ- በሃሳብ የተለየን ወንድማችን
አፈር ሳይሆን
እናት አሳዝነን- ለአባት ማቅ አልብሰን
እርር አርገን
ልጆች ከጉያ- ተነጥቀው
ለመቃብር -ተዳርገው
ዋይታ በዝቶ- ለቅሶ ቢሆን
ዘፈን ጠፍቶ -ሳቃችን ሆኖ ሃዘን
ሺህዎች -እንደቅጠል ቢረግፉ
ቢበዛብን -የእኛው በእኛ- ፍጡር ግፉ
አኬልዳማ ሆነ ቃሉ- አኬልዳማ
የሞት ጥላ አጥልቶብን-የእልቂታችን ካራማ።
እኛው በእኛ ላይ- ከፍተን
እንደ ወንድማማች- በሰላም አብረን
መኖር ተሳነንና-ቀጠለ ጥፋታችን።
ዛሬም እንደትናንቱ- በሃሳብ ለተለየን
ይሙት በቃ- ብለን በየን
እንደ ፋንታ በላይ- ሁሉ
ይሙት አልን ሙሉነህ- ይሙት አልን ብርሃኑ
እንደ መርዕድ እና አመሃ- ደምሴና ቁምላቸው
ፈረድን-
ይሙት በቃ በመስፍን
በመላኩና በአንዳርጋቸው።
መደብን ከመደብ- ጎሣን ከጎሣ ሆነ ብለን
ኃይማኖትን ከኃይማኖት- በማጋጨት ተክነን
ከጎሰኝነት ከሃይማኖት ከመደብ ወገንተኝት
መጽዳት አቅቶን
በኢትዮጵያዊነት ጥላ ስር -ማረፍ ወንጀል ሆኖ
ደም ይፈሳል ጅረት ሆኖ- ቱግ ብሎ
የጥቂቶች ፍላጎት- በአብዛኞቻችን ጀርባ ተጭኖ
አሜን ብለን እንድንኖር- ህግ ህኖ
መልካም ስራ ተንቆ
ወንጀል በተገላቢጦሽ
መልካም ተብሎ
የምንኖርባት ምድር- ሆናለች አኬልዳማ
የሞት ጥላ ያጠለባት- የጥላቻ ካራማ
ልዩነታችን የሚፈታው- ሆነና በጠመንጃ
ገዥ ሆኖ አፈሙዝ- ግኡዝ ፍጡሩ ሳንጃ
የትኛው ጅኒ- አጋንንት ቢያርፍብን ነው
ምድራችን ለዓመታት- አኬልዳማ የሆነው?
መቸ ይሆን የሚቆመው
እኛው በእኛ ላይ የፈጠርነው
መከራው?
ዳግማዊ ዳዊት
ታህሳስ 2002 ዓ.ም.
Ethio_dagmawi@yahoo.com
ምነው አልቆም አለ-አላበቃ
ርህራሄ ተነፍጎት-
እየኖረ በዋይታ
ስው ባምሳያው- ሰብዓዊነት
አልሰማው ብሎ-ኃላፊነት
ሰብዓዊ መብቱ- ተረግጦ
ወገን በወገን ላይ-ዶልቶ
ወገን ሞቶ-ወገን ገድሎ
በፉከራ
ፈጣሪም ሳይፈራ
ዘራፍ ብለን ራሳችን- በራሳችን
እኛው በእኛ ላይ- አምፀን
ጳጳስ ገድለን- ጳጳስ ሾመን
አሃዱ ብለን በስልሳ ራስ- አንገት ቀልተን
የኛን ራስ- እኛው ጠልተን
የአስራ ሁለት ዓመት ልጅ -ገና ጨቅላ
የአስር ዓመት ልጃገረድ- እምቦቅላ
ሽኘን በሞት- በሽለላ
ገዳይ ብለን በፉከራ።
ድንበር ሰርተን- ሸሁን ገፍተን- ካህን ጠልተን
በማናውቀው ርዕዮተዓለም- ተጠምቀን
ሽብር ሆኖ ቀይና ነጭ-ወገን ከፍሎ
አንዱ ሌላውን-ሊያጠፋ ተገዝቶ ምሎ
ልንጠፋፋ-ተገዳድረን
በጥፋት ካህን ፊት-ምለን ተገዝተን
ላንተኛ- በሃሳብ የተለየን ወንድማችን
አፈር ሳይሆን
እናት አሳዝነን- ለአባት ማቅ አልብሰን
እርር አርገን
ልጆች ከጉያ- ተነጥቀው
ለመቃብር -ተዳርገው
ዋይታ በዝቶ- ለቅሶ ቢሆን
ዘፈን ጠፍቶ -ሳቃችን ሆኖ ሃዘን
ሺህዎች -እንደቅጠል ቢረግፉ
ቢበዛብን -የእኛው በእኛ- ፍጡር ግፉ
አኬልዳማ ሆነ ቃሉ- አኬልዳማ
የሞት ጥላ አጥልቶብን-የእልቂታችን ካራማ።
እኛው በእኛ ላይ- ከፍተን
እንደ ወንድማማች- በሰላም አብረን
መኖር ተሳነንና-ቀጠለ ጥፋታችን።
ዛሬም እንደትናንቱ- በሃሳብ ለተለየን
ይሙት በቃ- ብለን በየን
እንደ ፋንታ በላይ- ሁሉ
ይሙት አልን ሙሉነህ- ይሙት አልን ብርሃኑ
እንደ መርዕድ እና አመሃ- ደምሴና ቁምላቸው
ፈረድን-
ይሙት በቃ በመስፍን
በመላኩና በአንዳርጋቸው።
መደብን ከመደብ- ጎሣን ከጎሣ ሆነ ብለን
ኃይማኖትን ከኃይማኖት- በማጋጨት ተክነን
ከጎሰኝነት ከሃይማኖት ከመደብ ወገንተኝት
መጽዳት አቅቶን
በኢትዮጵያዊነት ጥላ ስር -ማረፍ ወንጀል ሆኖ
ደም ይፈሳል ጅረት ሆኖ- ቱግ ብሎ
የጥቂቶች ፍላጎት- በአብዛኞቻችን ጀርባ ተጭኖ
አሜን ብለን እንድንኖር- ህግ ህኖ
መልካም ስራ ተንቆ
ወንጀል በተገላቢጦሽ
መልካም ተብሎ
የምንኖርባት ምድር- ሆናለች አኬልዳማ
የሞት ጥላ ያጠለባት- የጥላቻ ካራማ
ልዩነታችን የሚፈታው- ሆነና በጠመንጃ
ገዥ ሆኖ አፈሙዝ- ግኡዝ ፍጡሩ ሳንጃ
የትኛው ጅኒ- አጋንንት ቢያርፍብን ነው
ምድራችን ለዓመታት- አኬልዳማ የሆነው?
መቸ ይሆን የሚቆመው
እኛው በእኛ ላይ የፈጠርነው
መከራው?
ዳግማዊ ዳዊት
ታህሳስ 2002 ዓ.ም.
Ethio_dagmawi@yahoo.com
Tuesday, October 13, 2009
አረንጓዴ ሰው
“ሕዝባችን ተስብሰብ-ለሰበሩ ዜና
ባለጸጋው ጻድቅ- መሆኑ ይሰማ
ይኸ ባለጸጋ- ይኸ ያገሬ ሰው
ይኸ ባለሆቴል- ይኸ ወርቅ አንጣሪው
የሥራ ዕድል ፈጥሮ- ልቤን አስደሰተው”
ብሎ ጋዜጠኛው -ፅፎ አነበብኩና
ስለዚህ ባለሃብት- ሃሴት አረግሁና
እኔም የበኩሌን-ለገስኩት ምስጋና
“አንደበት ይከፈት-ጆሮወች ያዳምጡ
ለዚህ ባላፀጋ- ሽልማቶች ይምጡ
በል እግዜሩም ስማ- ፅድቅ ተለውጧል
ከዛሬ መነኩሴ- ባላፀጋ በልጧል
“ፀሃይ ትቁምለት- ትዘግይ ጨረቃ
ይኸ ባለፀጋ- እስኪል ድረስ በቃ
እስከሚበዛለት -ሃብቱ እስከሚስፋፋ
ሌሊቱም ቀን ይሁን -ብርሃን አይጥፋ።”
ብዬ ምስጋናየን- ሳዥጎደጉደው
ይኸ የአጎቴ ልጅ-የተበሳጨው
ከእኔ የተለየ-ሚስጥር ያውቅ ኖሮ
እንዲህ ሲል ነገረኝ-ሃሳቡን ቀምሮ።
“ለተራበ ማብላት-ለታረዘ ማልበስ
ታማሚ ማጽናናት-ለችግርም መድረስ
መጾም መፀለዩ-ቅንነት ማሰቡ
መች ሆኖ ተገኘ- የዛሬ ሰው ግቡ!
“ከደሃ ቀምቶ- ከደካማ ዘርፎ
ቢኖርም ቢሞላም- ተርፎ ተትረፍርፎ
ወርቅና አልማዝ ይዞ- ነዳጅ አስቆፍሮ
ሆኖ መገኘት ነው-ካለመጠን ከብሮ
ሰውን ሰው ያሰኘው- የለየው ዘንድሮ።
“የስው ልጅ ሲፈጠር- በጌታዬ አምሳያ
ነበረ ለታላቅ- ለክብር ማሳያ
ዛሬ የስው ልጆች- ወረቀትን ፈጥረው
ቁጥር ጽፈውበት- አንድ ሁለት ብለው
አረንጓዴ ቀለም- ቅርጻ ቅርጹን ስለው
ከራሳቸው በላይ- ለብር ክብር ሰጥተው
መኖር ጀምረዋል-ከሱ በታች ሆነው።
…
“መልኩን ሳፈላልግ- ጠይም ወይም ቀዩን
ቀረና የእርሱነት- መምሰል አምሳያውን
ንዋየ ፀሎቱ- ገንዘብ ሆኖ አምላኩ
አረንጓዴ ሆኗል- ባለጸጋው መልኩ።
…
“አንተን መሳይ ሰወች- እናንት ኋላ ቀሮች
ጠይምና ጥቁር-ቀይ አመላካቾች
ልታውቁ ይገባል- የዛሬን እውነታ
በጠይም በጥቁር- በቀይ ሰው ፋንታ
የሰው ልጅ ውበቱ- የሚያምር ቁመናው
አረንጓዴ ሆኗል- የእርሱ ሁለመናው።
“ገንዘቡ ዳኛ ነው- ፖሊስም ጠበቃ
ሃይሉ ልክ የሌለው- ተቆጥሮ አያበቃ
ፍትህና ክብር -ገዥ በገንዘቡ
ይኸ ባለጸጋ- ባለ ወርቅ ቅቡ
ሕጻን ሴት ያገባው- ሕፃን እቁባቱ
የስው ሚስት የቀማው- አድርጎት መብቱ
ሁሉ ሰው ጌታዬ- ብሎ የሚጠራው
እርሱን ነው የሚያደንቅ- ጋሸ ጋዜጠኛው።
ብሎ ተናገረ- ይኸ የአጎቴ ልጅ
ስለ አረንጓዴው ሰው- ለሁሉ እንደማይበጅ።
ትናንት ህጻን ሆኘ-ሳድግ በሰፈሬ
የሰው ልጅ መጠሪያው- ልዩ ነው ከዛሬ
አይደለ በልብሱ- በፀጋ በሃብቱ
አይደል በቁመናው- ተክለ-ሰውነቱ
አይደል በትምህርቱ- በዕውቀት ሊቅነቱ
ሰው በሰውነቱ- ሲለካ የማውቀው
ፍጹም ልዩ ነበር- ዛሬ ከምናየው።
አንገቱን ለፍትህ- አንደበቱ ለእውነት
ውሸትን የጠላ- ግፍን የሚጋፈጥ
ከክፎወች ሸንጎ- ፈጽሞ የራቀ
አንቱ የተባለ-በአገር የታወቀ
ነበር የሰው መልኩ-ለእውነት መቆሙ
ትናንት የምናውቀው- የሰው ልጅ መልካሙ
ዛሬ ተለየና -ውበት ተቀይሮ
ዓይናችን የሚያየው- ብር ሆነ ዘንድሮ።
እስኪመለስ ድረስ -አይንም ወደ ድሮው
ስንናፍቅ ከዋልን- ገንዘብን እንደሰው
እውነትም ይዛባል-ፍትህ ይሰወራል
ገንዘብ የአገር ዳኛ- ጠበቃ ይሆናል
…
አንተ ጋዜጠኛ- አንተ ወሬ አቀባይ
እስኪ እንደ አጎቴ ልጅ-አንተም እውነቱን እይ
ያ ባለጸጋ ሰው- በዓለም የከበረ
እውነቱን አሰማን- ማን እንደነበረ?
ዳግማዊ ዳዊት
ጥቅምት 2002
Ethio_dagmawi@yahoo.com
ባለጸጋው ጻድቅ- መሆኑ ይሰማ
ይኸ ባለጸጋ- ይኸ ያገሬ ሰው
ይኸ ባለሆቴል- ይኸ ወርቅ አንጣሪው
የሥራ ዕድል ፈጥሮ- ልቤን አስደሰተው”
ብሎ ጋዜጠኛው -ፅፎ አነበብኩና
ስለዚህ ባለሃብት- ሃሴት አረግሁና
እኔም የበኩሌን-ለገስኩት ምስጋና
“አንደበት ይከፈት-ጆሮወች ያዳምጡ
ለዚህ ባላፀጋ- ሽልማቶች ይምጡ
በል እግዜሩም ስማ- ፅድቅ ተለውጧል
ከዛሬ መነኩሴ- ባላፀጋ በልጧል
“ፀሃይ ትቁምለት- ትዘግይ ጨረቃ
ይኸ ባለፀጋ- እስኪል ድረስ በቃ
እስከሚበዛለት -ሃብቱ እስከሚስፋፋ
ሌሊቱም ቀን ይሁን -ብርሃን አይጥፋ።”
ብዬ ምስጋናየን- ሳዥጎደጉደው
ይኸ የአጎቴ ልጅ-የተበሳጨው
ከእኔ የተለየ-ሚስጥር ያውቅ ኖሮ
እንዲህ ሲል ነገረኝ-ሃሳቡን ቀምሮ።
“ለተራበ ማብላት-ለታረዘ ማልበስ
ታማሚ ማጽናናት-ለችግርም መድረስ
መጾም መፀለዩ-ቅንነት ማሰቡ
መች ሆኖ ተገኘ- የዛሬ ሰው ግቡ!
“ከደሃ ቀምቶ- ከደካማ ዘርፎ
ቢኖርም ቢሞላም- ተርፎ ተትረፍርፎ
ወርቅና አልማዝ ይዞ- ነዳጅ አስቆፍሮ
ሆኖ መገኘት ነው-ካለመጠን ከብሮ
ሰውን ሰው ያሰኘው- የለየው ዘንድሮ።
“የስው ልጅ ሲፈጠር- በጌታዬ አምሳያ
ነበረ ለታላቅ- ለክብር ማሳያ
ዛሬ የስው ልጆች- ወረቀትን ፈጥረው
ቁጥር ጽፈውበት- አንድ ሁለት ብለው
አረንጓዴ ቀለም- ቅርጻ ቅርጹን ስለው
ከራሳቸው በላይ- ለብር ክብር ሰጥተው
መኖር ጀምረዋል-ከሱ በታች ሆነው።
…
“መልኩን ሳፈላልግ- ጠይም ወይም ቀዩን
ቀረና የእርሱነት- መምሰል አምሳያውን
ንዋየ ፀሎቱ- ገንዘብ ሆኖ አምላኩ
አረንጓዴ ሆኗል- ባለጸጋው መልኩ።
…
“አንተን መሳይ ሰወች- እናንት ኋላ ቀሮች
ጠይምና ጥቁር-ቀይ አመላካቾች
ልታውቁ ይገባል- የዛሬን እውነታ
በጠይም በጥቁር- በቀይ ሰው ፋንታ
የሰው ልጅ ውበቱ- የሚያምር ቁመናው
አረንጓዴ ሆኗል- የእርሱ ሁለመናው።
“ገንዘቡ ዳኛ ነው- ፖሊስም ጠበቃ
ሃይሉ ልክ የሌለው- ተቆጥሮ አያበቃ
ፍትህና ክብር -ገዥ በገንዘቡ
ይኸ ባለጸጋ- ባለ ወርቅ ቅቡ
ሕጻን ሴት ያገባው- ሕፃን እቁባቱ
የስው ሚስት የቀማው- አድርጎት መብቱ
ሁሉ ሰው ጌታዬ- ብሎ የሚጠራው
እርሱን ነው የሚያደንቅ- ጋሸ ጋዜጠኛው።
ብሎ ተናገረ- ይኸ የአጎቴ ልጅ
ስለ አረንጓዴው ሰው- ለሁሉ እንደማይበጅ።
ትናንት ህጻን ሆኘ-ሳድግ በሰፈሬ
የሰው ልጅ መጠሪያው- ልዩ ነው ከዛሬ
አይደለ በልብሱ- በፀጋ በሃብቱ
አይደል በቁመናው- ተክለ-ሰውነቱ
አይደል በትምህርቱ- በዕውቀት ሊቅነቱ
ሰው በሰውነቱ- ሲለካ የማውቀው
ፍጹም ልዩ ነበር- ዛሬ ከምናየው።
አንገቱን ለፍትህ- አንደበቱ ለእውነት
ውሸትን የጠላ- ግፍን የሚጋፈጥ
ከክፎወች ሸንጎ- ፈጽሞ የራቀ
አንቱ የተባለ-በአገር የታወቀ
ነበር የሰው መልኩ-ለእውነት መቆሙ
ትናንት የምናውቀው- የሰው ልጅ መልካሙ
ዛሬ ተለየና -ውበት ተቀይሮ
ዓይናችን የሚያየው- ብር ሆነ ዘንድሮ።
እስኪመለስ ድረስ -አይንም ወደ ድሮው
ስንናፍቅ ከዋልን- ገንዘብን እንደሰው
እውነትም ይዛባል-ፍትህ ይሰወራል
ገንዘብ የአገር ዳኛ- ጠበቃ ይሆናል
…
አንተ ጋዜጠኛ- አንተ ወሬ አቀባይ
እስኪ እንደ አጎቴ ልጅ-አንተም እውነቱን እይ
ያ ባለጸጋ ሰው- በዓለም የከበረ
እውነቱን አሰማን- ማን እንደነበረ?
ዳግማዊ ዳዊት
ጥቅምት 2002
Ethio_dagmawi@yahoo.com
Friday, September 11, 2009
ጥጃ- ለዘመን መለወጫ
በግንባሩ ወግቶ- ቢያጠቃኝ በርግጫ
ቢላ ቢላዋ አለኝ- ለዚህ ክፉ ጥጃ።
ዘመን ተለውጦ-ዘመኑ እስኪተካ
“ይወርዳል… ይለቃል”- ወሬ እንዳልተቦካ
ይኸ ጥጃ እምቢ አለ- አልሄድ ብሏል ለካ!
ሰፈሩን አመሰው-አጉል ተፈራግጦ
ሰው ግራ ገባው- በጭንቀት ተውጦ
እረኛ አይመልሰው-አዳኝ አያድነው
ሰውን እየጎዳ-ከአካል እያወጣው
ለህልፈት ሲዳርግ- እፎይታ ሲያሳጣ
ኑሮን ክፉ ትርኢት- ሲያበዛበት ጣጣ
ምን ጉድ ሆነ እና ነው- ይህ የሰፈር ጥጃ
ጀግና የለም እንዴ-የሚያውቅ ጠመንጃ።
እናንት አድርባዮች- ዘመን ስትለውጡ
ከዚህ ክፉ ጥጃ- አብራችሁ አትውጡ
ብትቀሩ ይሻላል- እናንተስ አትምጡ።
እናንት ወገኖቼ- ከብት የምታረቡ
ይህን ክፉ ጥጃ- ከእናንተ አትደንቡ
እናንተ ተለዩ- ወደተራራው
ያ ክፉ ጥጃ ነው- ገደል የሚያምረው።
አጨደው ሰርዶውን- የሰፈሩን ሙጃ
ምላሱ መርዝ አለው- እግሩ የጦር ሳንጃ
ረሃብ ላይ ጣለው-ፍየልና በጉን
አጉልኛ ጠባት- ያች ደግ እናቱን
ጀግና ምነው ጠፋ- የሚያድን ላሚቱን።
ቄራ ሰራተኞች-በግ የምታግዙ
እስኪ በዚህ ዓመት-ይህን ጥጃ ግዙ
ገበያ ውሰዱት-ለዚህ አዲስ ዓመት
አራጅእንዲወስደው- ሁሉን የሚያውቅበት
አቅርበው ለሽያጭ-ሲራራው ነጋዴ
በሰላም ልተኛ-ይረፍልኝ ሆዴ።
ከሰሜን ከምስራቅ- ከምዕራብ ከደቡብ
ተሰባሰብና- ሁሉም ያገሬ ህዝብ
ደስ ብሎን እንድንውል- ዘመን መለወጫ
ጨፌ ጎዝጉዛችሁ- ቄጠማ ወይ ሙጃ
አንገቱ ላይ አርጉ- ቢላዋ ወይ ሳንጃ
ገላግሉን በአንድዬ- ከዚህ ክፉ ጥጃ።
ዳግማዊ ዳዊት
መስከረም 2002 ዓ.ም.
ቢላ ቢላዋ አለኝ- ለዚህ ክፉ ጥጃ።
ዘመን ተለውጦ-ዘመኑ እስኪተካ
“ይወርዳል… ይለቃል”- ወሬ እንዳልተቦካ
ይኸ ጥጃ እምቢ አለ- አልሄድ ብሏል ለካ!
ሰፈሩን አመሰው-አጉል ተፈራግጦ
ሰው ግራ ገባው- በጭንቀት ተውጦ
እረኛ አይመልሰው-አዳኝ አያድነው
ሰውን እየጎዳ-ከአካል እያወጣው
ለህልፈት ሲዳርግ- እፎይታ ሲያሳጣ
ኑሮን ክፉ ትርኢት- ሲያበዛበት ጣጣ
ምን ጉድ ሆነ እና ነው- ይህ የሰፈር ጥጃ
ጀግና የለም እንዴ-የሚያውቅ ጠመንጃ።
እናንት አድርባዮች- ዘመን ስትለውጡ
ከዚህ ክፉ ጥጃ- አብራችሁ አትውጡ
ብትቀሩ ይሻላል- እናንተስ አትምጡ።
እናንት ወገኖቼ- ከብት የምታረቡ
ይህን ክፉ ጥጃ- ከእናንተ አትደንቡ
እናንተ ተለዩ- ወደተራራው
ያ ክፉ ጥጃ ነው- ገደል የሚያምረው።
አጨደው ሰርዶውን- የሰፈሩን ሙጃ
ምላሱ መርዝ አለው- እግሩ የጦር ሳንጃ
ረሃብ ላይ ጣለው-ፍየልና በጉን
አጉልኛ ጠባት- ያች ደግ እናቱን
ጀግና ምነው ጠፋ- የሚያድን ላሚቱን።
ቄራ ሰራተኞች-በግ የምታግዙ
እስኪ በዚህ ዓመት-ይህን ጥጃ ግዙ
ገበያ ውሰዱት-ለዚህ አዲስ ዓመት
አራጅእንዲወስደው- ሁሉን የሚያውቅበት
አቅርበው ለሽያጭ-ሲራራው ነጋዴ
በሰላም ልተኛ-ይረፍልኝ ሆዴ።
ከሰሜን ከምስራቅ- ከምዕራብ ከደቡብ
ተሰባሰብና- ሁሉም ያገሬ ህዝብ
ደስ ብሎን እንድንውል- ዘመን መለወጫ
ጨፌ ጎዝጉዛችሁ- ቄጠማ ወይ ሙጃ
አንገቱ ላይ አርጉ- ቢላዋ ወይ ሳንጃ
ገላግሉን በአንድዬ- ከዚህ ክፉ ጥጃ።
ዳግማዊ ዳዊት
መስከረም 2002 ዓ.ም.
Subscribe to:
Posts (Atom)